የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከፓኪስታን ባለሃብቶች ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ

1 Yr Ago
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከፓኪስታን ባለሃብቶች ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከፓኪስታን ባለሃብቶች ጋር የመግባቢያ ሰነድ መፈራረሙን አስታወቀ።
ስምምነቱ የፋርማሲዩቲካልስ፣ የማሸጊያ ምርቶች ፋብሪካ እና የኢንዱስትሪ ፓርክ ማሳደግ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን ያለመ መሆኑን ከኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡
ሥምምነቱም የፓኪስታን ባለሃብቶች ቡድን በኢትዮጵያ እያደረገ ያለው ጉብኝት አካል መሆኑም ተመላክቷል፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው አስቻይ የኢንቨስትመንት ሁኔታዎች እና በፓኪስታን ስራ ፈጣሪዎች መካከል ያለው ሰፊ የቴክኖሎጅ እና በዘርፉ ያላቸው የዳበረ ልምድ ለስምምነቱ አስተዋፅኦ ማድረጋቸውም ተነግሯል፡፡

ተያያዥ ርዕሶች

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top