በህንድ ለብቻቸው የምርጫ ጣቢያ የተቋቋመላቸው መነኩሴ

11 ቀን በፊት
በህንድ ለብቻቸው የምርጫ ጣቢያ የተቋቋመላቸው መነኩሴ
በህንድ በጫካ ውስጥ የሚኖሩ የአንድን መነኩሴ የመምረጥ መብት ለማረጋገጥ ሲባል ለብቻቸው የምርጫ ጣቢያ ተቋቁሞላቸዋል።
 
969 ሚሊዮን ዜጎች ድምጽ ለመስጠት የተዘጋጁበት የህንድ ምርጫ እየተካሄደ ሲሆን፤ በዓለማችን ለብዙ ቀናት የሚከናወን ግዙፉና ውዱ ምርጫም ነው።
 
በሀገረ ህንድ የአንድን መነኩሴ ዴሞክራሲያዊ የመምረጥ መብት ለማረጋገጥ የተሄደበት ርቀት አንድ ድምጽ ያለው ዋጋ ምን ያህል እንደሆነ የሚያሳይም ነው ተብሏል፡፡
 
የምርጫ ሕጎች እያንዳንዱ መራጭ ከድምጽ መስጫ ጣቢያው ከ2 ኪሎ ሜትር በላይ እንዳይርቅ ይጠይቃሉ።
 
በጉጅራት ግዛት ጅር ጥብቅ ደን ውስጥ ለሚኖሩ አንድ የሂንዱ መነኩሴ የመምረጥ ዕድል ለመስጠት ፤ የምርጫ አስፈፃሚ ባለሙዎች ረጅም እና አስቸጋሪ በሆነ መንገድ በአውቶቡስ የሚደረግ ጉዞን ጨምሮ የሁለት ቀናት ጉዞ አድርገዋል።
 
የጅር ጫካ በህንድ በጣም አደገኛ የኢዤያ አንበሶች የሚኖሩበትና ከፍተኛ ጥበቃ ከሚደረግላቸው ደኖች ውስጥ አንዱ ነው፡፡
 
ማሃንት ሃሪደስ ኡዲሴን የተባሉ የሂንዱ መነኩሴ በዚህ ደን ውስጥ በመኖሪያ አካባቢያቸው ሙሉ የመምረጥ መብታቸው ተረጋግጦላቸዋል ነው የተባለው፡፡
 
አጋማሽ ላይ የሚገኘው የህንድ ምርጫ ታሪክዊና ሀገሪቱ ከፍተኛ የዴሞክራሲ ልምምድ ላይ እንደሆነች ያሳየችበት ነው ተብሎለታል፡፡
 
መራጮች በሀገሪቱ የትኛውም አካባቢ ቢሆኑ የመምረጥ መብታቸውን እንዲያረጋግጡ እየተጋች ትገኛለች ብሏል አልጀዚራ በዘገባው፡፡

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top