የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ አመራሮች እና አባላት የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎበኙ

155 Days Ago
የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ አመራሮች እና አባላት የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎበኙ

የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ አመራሮች እና የሰራዊት አባላት የዓድዋ ድል መታሰቢያን በዛሬው ዕለት ጎብኝተዋል።

በጉብኝታቸውም፤ የዓድዋ ድል መታሰቢያ ኢትዮጵያ ለአንድነቷ እና ለሉዓላዊነቷ ታላቅ መስዋዕትነት እና ገድል የተሰራላት ትልቅ የጀግንነት ታሪክም ያላት ሀገር መሆኗ የታየበት ነው ብለዋል፡፡

መታሰቢያው የአልበገር ባይነትን፤ የአንድነት፤ የነጻነት ፋና ወጊ እኛ ኢትዮጵያውያኖች እንደመሆናችን መጠን ይህን ተግባር ለትውልድ ለማሻገር መከላከያ ሰራዊታችን ለትውልድ የሚሰራው ተግባር ነው ሲሉም ገልጸዋል፡፡ 

የዓድዋ ድል መታሰቢያ እንደ መከላከያ ሰራዊት በአባቶቻችን ጀግንነት እንድንኮራ የሚያደርግ ከመሆኑም በላይ ልዩ የሞራል እና የአገር አደራ ስንቅ የሚሰጥ ነውም ማለታቸውን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።


አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ግብረመልስ
Top