የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ የምስራቅ አፍሪካ አርብቶ አደሮች ኤክስፖን ጎብኝተዋል፡፡
በጉብኝቱ ላይ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አይሻ መሃመድ (ኢ/ር) እና ሌሎች የሥራ ሃላፊዎች መሳተፋቸውን ከመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
የምስራቅ አፍሪካ አርብቶ አደሮች ኤክስፖ "አርብቶ አደርነት የምስራቅ አፍሪካ ኅብረቀለም" በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል፡፡