የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት መስተዳድር ምክር ቤት የሰላም አማራጭ ተቀብለው የተመለሱ እና በተለያዩ የመንግሥት መዋቅር ስር ሲያገለግሉ የነበሩ የቀድሞው የመንግሥት ሰራተኞች ወደ መንግሥት ስራቸው እንዲመለሱ ውሳኔ አሳልፏል።
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት መስተዳድር ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል።
ምክር ቤቱ በስብሰባው የሰላም አማራጭን ተቀብለው በተመለሱና ቀደም ሲል በተለያዩ የመንግሥት መዋቅሮች ሲያገለግሉ በነበሩ ሠራተኞች ላይ ውሳኔ አሳልፏል።
የክልሉ መንግሥት ሰላምን ለማጽናትና ልማትን ለማረጋገጥ ባለው ጽኑ ቁርጠኝነት፣ ታጥቀው ለሚንቀሳቀሱ አካላት በተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ሲያቀርብ መቆየቱ ይታወሳል።
በዚህም መሠረት በመንግሥት ጥሪ፣ በድርድርና በውይይት የሰላም አማራጭን መርጠው የተመለሱና የተሃድሶ ሥልጠና የወሰዱ የቀድሞ የመንግሥት ሠራተኞች ወደ መደበኛ ሥራቸው እንዲመለሱ ምክር ቤቱ ወስኗል።
ይህ ውሳኔ የክልሉ መንግሥት ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታትና ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ያለውን ዝግጁነት የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል።
በቀጣይም ለክልሉ ዕድገትና አንድነት መሰል የሰላም ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተመላክቷል።
በራሄል ፍሬው
#EBC #Ethiopia #AmharaRegion #PeaceProcess #CivilService #NationalUnity #PeaceInitiative