ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለተሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሙሉ ልባዊ አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
ፍትሐዊ፣ ነጻ እና ግልጽነት የተሞላበት ምርጫ በማካሄድ “ለህዝባችን የተገባውን ቃል ላሳካው” ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድም ፕሬዚዳንቱ ምስጋና አቅርበዋል።

የሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ ታዛቢዎችም “በዴሞክራሲ ጉዟችን ላይ እምነት ስለጣሉ” አመሰግናቸዋለሁ ብለዋል ፕሬዚዳንት ታየ በማኅበራዊ ትስስር ገጽ ባጋሩት መልዕክት።