የኢራን ማዕከላዊ ወታደራዊ ዕዝ እስራኤል በደቡባዊ ሊባኖስ የምትፈጽመው ጥቃት ከአሜሪካ ጋር የተደረሰውን ስምምነት የሚጥስ በመሆኑ የሆርሙዝ ሰርጥን መዝጋቱን አስታውቋል።
የኢራን አብዮታዊ ዘብ ባሕር ኃይል የባሕር መተላለፊው ለሁሉም መርከቦች በመዘጋቱ ማናቸውም መርከቦች የወደ ሰርጡ የሚቀርቡ ከሆነ ለአደጋ ስለሚጋለጡ መርከባቸውን ከሆርሙዝ እንዲያርቁ አስጠንቅቋል።

አብዮታዊ ዘቡ በአገሪቱ ቴሌቪዥን በቀረበው መግለጫ ላይ አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት መድረሳቸውን ተከትሎ አርብ ዕለት ሙሉ ለሙሉ የተከፈተው ወሳኙ የባሕር ላይ መተላለፊያ ለሁሉም መርከቦች ዝግ እንደሚሆን አሳውቋል።
ኢራን ከአሜሪካ ጋር በደረሰችው የመግባቢያ ስምምነት ላይ እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምታካሂደው ተከታታይ ጥቃት እንደሚቆም የተገለጸ ቢሆንም ግጭቱ በመቀጠሉ ኢራን ስምምነቱ ተጥሷል ማለቷን የቢቢሲ እና አልጀዚራ ዘገባ ያመለክታል።