Search

ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ የአገልግሎት ዘመናቸውን ላጠናቀቁት አምባሳደር ባጫ ደበሌ ሽኝት አደረጉ

ረቡዕ ነሐሴ 27, 2018 142

የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ የአገልግሎት ዘመናቸውን አጠናቀው ለሚመለሱት በኬንያ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ባጫ ደበሌ በናይሮቢ በሚገኘው ቤተ መንግስት ይፋዊ ሽኝት አድርገዋል።

ፕሬዝዳንት ሩቶ በአሸኛኘት መርኃ ግብሩ ላይ፤ የሁለቱ ሀገራት፣ የመንግስታቱ እና የከፍተኛ አመራሩ የወደፊት ግንኙነት እና ወዳጅነት እጅግ በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝና ባለፉት አራት ዓመታት የበለጠ እየተጠናከረ መምጣቱን ገልፀዋል።

የሁለቱን ሀገራት የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትስስር፣ የድንበር አካባቢ ደህንነት እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል በትኩረት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።

 

በሽኝት ስነ-ስርዓቱ ላይ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ለአምባሳደር ባጫ ደበሌ ቀጣይ የስራ ዘመናቸው የስኬትን እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: