Search

ኤር ቻይና ወደ ፒዮንግያንግ የቀጥታ በረራ ጀመረ

ሰኞ መጋቢት 21, 2018 54

የቻይናው ብሔራዊ አየር መንገድ ኤር ቻይና በቤጂንግ እና በሰሜን ኮሪያ መዲና ፒዮንግያንግ መካከል ተቋርጦ የነበረውን የቀጥታ በረራ ከዛሬ ጀምሮ በይፋ መጀመሩን አስታውቋል።
በአየር መንገዱ ድረ-ገጽ ላይ የወጣው መረጃ እንደሚያመላክተው፣ በረራ ቁጥር CA121 በቤጂንግ ሰዓት አቆጣጠር ማለዳ 2:05 ላይ ከቤጂንግ ካፒታል ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተነስቷል።
ይህ በረራ በሰሜን ኮሪያ የአካባቢ ሰዓት አቆጣጠር ረፋድ 5:00 ገደማ ፒዮንግያንግ አየር ማረፊያ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል የተጀመረው ይህ የቀጥታ በረራ በቤጂንግ እና በፒዮንግያንግ መካከል ያለውን የጉዞና የትራንስፖርት ትስስር ዳግም የሚያጠናክር መሆኑ ተመላክቷል።