የዜጎችን አኗኗር ምቹ እና ዘመናዊ ማድረግ የኮሪደር ልማት መርሐ-ግብራችን ዋነኛ ግብ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ ባሰፈሩት መልዕክት፣ "ያየነው የአርባ ምንጭ ከተማ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ዘመናዊ የአስፋልት መንገድ እና መብራቶችን እና ዲጂታል ስክሪኖችን ያካተተ ሲሆን በተጠናቀቁት የኮሪደር ሥራዎች ላይ አገልግሎቱ ተጀምሯል" ብለዋል።
"ጥራቱን የጠበቀ ዘመናዊ መሠረተ-ልማትን ከአረንጓዴ ልማት ጋር በማስተሳሰር የከተሞቻችንን ምቹነት የማረጋገጥ ስራችን ተጠናክሮ ይቀጥላል" ሲሉም አክለዋል።