Search

በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተማሪዎች የ2019 የትምህርት ዘመንን ጀመሩ

ማክሰኞ መስከረም 05, 2019 149

በአማራ፣ በሲዳማ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች፣ እንዲሁም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ሶዶ ከተማ 2019 . መደበኛ የመማር ማስተማር ሥራ በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀምሯል።

በዚህም በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አዲስ እና ነባር ተማሪዎች ከክረምት ዕረፍት መልስ ወደ ትምህርት ገበታቸው ተመልሰዋል።

በአማራ ክልል በአጠቃላይ 4.8 ሚሊዮን ተማሪዎች ለዘንድሮው የትምህርት ዘመን የተመዘገቡ ሲሆን በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች የመማር ማስተማር ሂደቱ ጀምሯል።

በሲዳማ ክልል ከቅድመ መደበኛ ጀምሮ እስከ 12 ክፍል የሚገኙ 1.3 ሚሊዮን ተማሪዎች ትምህርታቸውን ጀምረዋል።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ደግሞ 320 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በመቀበል በተለያዩ የግል እና የመንግሥት ትምህርት ቤቶች ትምህርት ተጀምሯል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ሶዶ ከተማ፣ 243 ትምህርት ቤቶች 67 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በመቀበል ትምህርት ተጀምሯል።

በተለያዩ ትምህርት ቤቶች የተገኙ ተማሪዎች፣ በመጀመሪያው ቀን በትምህርት ገበታ ላይ መገኘታቸው ለዓመቱ ስኬት ስንቅ እንደሚሆናቸው ተናግረዋል።

ተማሪዎች የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በቂ ዝግጅት አድርገው መምጣታቸውን ገልጸዋል።

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: