ሩሲያ ከባይኮኑር ኮስሞድሮም ወደ ዓለም አቀፍ የጠፈር ጣቢያ ያመጠቀችው ፕሮግረስ ኤምኤስ-32 የጭነት መንኮራኩር በተሳካ ሁኔታ ወደ ተዘጋጀላት ምህዋር መግባቷን የሩሲያ መንግስታዊ የጠፈር ኮርፖሬሽን ሮስኮስሞስ አስታውቋል።
ሮስኮስሞስ ባወጣው መግለጫ ላይ "የመንኮራኩሩ ወደ ተዘጋጀለት ምህዋር መግባት፣ ከሮኬቱ ሶስተኛ ክፍል መለየቱ እና የአንቴናዎችና የፀሐይ ኃይል ሰሌዳዎች መዘርጋት በተያዘለት እቅድ መሰረት ተፈጽሟል" ብሏል።
የጭነት መንኮራኩሩ ቅዳሜ ዕለት በሞስኮ ሰዓት አቆጣጠር 20:27 ላይ ከዓለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ የሩሲያ ክፍል ዝቬዝዳ ሞጁል ጋር እንደሚጣበቅ ይጠበቃል።
እንደ ሮስኮስሞስ ገለጻ፣ መንኮራኩሩ የመጠጥ ውሃ፣ ለጣቢያው የሚያገለግል ነዳጅ፣ የጣቢያውን ከባቢ አየር ለመሙላት የሚያገለግል አየር እና የሳይንስ መሳሪያዎችን ጨምሮ ከ2.5 ቶን በላይ ጭነት ወደ ጣቢያው ያደርሳል።
በሰለሞን ገዳ