Search

ሩሲያ በልዩ ሁኔታ የምታከብረው የሁለተኛው ዓለም ጦርነት የድል ቀን

ሩሲያ የሁለተኛ ዓለም ጦርነት የድል ዕለትን በየዓመቱ ሜይ 9 በሞስኮ የሚገኘው ቀዩ አደባባይ በደማቅ ወታደራዊ ትርዒት ታከብራለች፡፡ ይህ የሩሲያ አከባበር በዓለም ላይ ካሉት ሀገራት ሁሉ እጅጉን የላቀ ድምቀት ያለው ነው። ይህ ታላቅ ትዕይንት “ሶቪየት ኅብረት” በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት “በናዚ” ላይ ድል መቀዳጀቷን የሚያስታውስ እና ሩሲያውያን ልዩ የሀገር ፍቅራቸውን የሚገልጹበት ነው። ሰልፉ ከድሉ መታሰቢያነቱ ባሻገርም እንደ ብሔራዊ የመታሰቢያ ቀን የሚታይ ሲሆን፣ ሩሲያ የጦር ኃይሏን አቅም እንዲሁም ታሪካዊ እና ጂኦፖለቲካዊ ትኩረቷ መግለጫ ሆኖም ያገለግላል።

“ናዚ” አውሮፓን በተቆጣጠረበት ወቅት እጅ ካልሰጡ ሀገራት መካከል ሩሲያውያን ይገኙበታል፡፡ የናዚ ጦር በመጀመሪያው ዙር ጦርነት የ”ሶቭየት ሕብረትን” ጦር አሸንፎ የነበረ ቢሆንም ሩሲያውያን ግን እንደገና ተደራጅተው 24 ሚሊዮን ዜጎቻቸውን ሰውተው አሸንፈዋል፡፡ ይህ የሩሲያ መስዋዕትነት ከ15 እስከ 17 ከሚሆነው የአውሮፓ ሀገራት መስዋዕትነት የላቀ ሲሆን፣ በጦርነቱ ምክንያት በመላው ዓለም ከተከፈለው የሰው ህይወት 40 በመቶውን እንደሚሸፍን የታሪክ ማስረጃዎች ያመላክታሉ፡፡

የመጀመሪያው የድል ሰልፍ በ”ሶቭየት ሕብረት” የተካሄደው “ናዚ” ከተሸነፈ ከአንድ ወር በኋላ እ.አ.አ ሰኔ 24 ቀን 1945 ነበር። በቀዩ አደባባይ በተካደው ሰልፍ ላይ ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ስታሊን የተገኙ ሲሆን፣ ማርሻል ጆርጂ ጁኮፍ በነጭ ፈረስ ላይ ተቀምጠው ሰልፉን መርተዋል።

በዚህ የመጀመሪያ ሰለፍ ላይ ከ40 ሺህ በላይ የሶቭየት ወታደሮች ተገኝተዋል፡፡ በዕለቱ በምርኮ ከተያዙ ወታደሮች የናዚ አርማዎችን የመጣል ሥነ ሥርዓት ተካሂዷል። ከሁሉም የሶቪየት ጦር ግንባር የተውጣጡ ወታደራዊ ክፍሎች እንዲሁም በጦርነቱ ውስጥ ጥቅም ላይ የዋሉ መሣሪያዎችም ለእይታ ቀርበውበታል።

ምንም እንኳ የመጀመሪያው ሰልፍ የተካሄደው በፈረንጆቹ ሰኔ ወር ቢሆንም ናዚ ለመጨረሻ ጊዜ እጁን የሰጠው እ.አ.አ ሜይ 8, 1945 በበርሊን