Search

ምክር ቤቱ የፕሬዝዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴን የመክፈቻ ንግግር የድጋፍ ሞሽን አዳመጠ

ሓሙስ መስከረም 29, 2018 112

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 1ኛ መደበኛ ስብሰባው ፕሬዝዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ ለሁለቱ ምክር ቤቶች ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ የቀረበን የድጋፍ ሞሽን አዳምጧል።

የድጋፍ ሞሽኑን አስመልክቶ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር የተከበሩ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) የመንግስት የተኩረት መስኮችን ለምክር ቤቱ አቅርበዋል፡፡

ምክር ቤቱ በመጀመሪያ አጀንዳም በ4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ስብሰባ ቃለጉባኤን መርምሮ በማጽደቅ ስብሰባውን ጀምሯል።

ምክር ቤቱ ከዚህ በመቀጠልም ፕሬዝዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ ለሁለቱ ምክር ቤቶች ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ የቀረበን የድጋፍ ሞሽን አዳምጧል።

የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም የመንግስትን የትኩረት ነጥቦችን አስመልክቶ ለህዝብ ተወካዮችና ለፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ መደበኛ ስብሰባ የመክፈቻ ንግግር ማቅረባቸው ይታወሳል፡፡

በመስከረም ቸርነት

#ebc #ebcdotstream #Ethiopia #etvparlama #parlama