Search

ኢትዮጵያ የዓለምን የባሕር ንግድ ሥርዓት ሙሉ በሙሉ መቀላቀል አለመቻሏ ለጉዳት አጋልጧታል - ፕሮፌሰር አደም ካሚል

ረቡዕ ጥቅምት 05, 2018 70

ምንም እንኳን ኢትዮጵያ ብዙ የተፈጥሮ ሀብቶች ቢኖሯትም በባሕር በር እጦት የዓለምን የባሕር ንግድ ሥርዓት ሙሉ በሙሉ መቀላቀል አለመቻሏ ለተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ጉዳቶች እያጋለጣት መሆኑን የታሪክ ተመራማሪው ፕሮፌሰር አደም ካሚል ገለጹ።

የባሕር በር ጥያቄ የመንግሥት ብቻ ሳይሆን የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ጥያቄ መሆኑንም አንስተው፤ ሕዝቡ በዘር፣ በቋንቋ፣ በሃይማኖት፣ በፖለቲካ አመለካከት ሳይከፋፈል በባሕር በር ጥያቄ ዙሪያ በአንድነት መቆም እንዳለበት አመላክተዋል።

“ቀይ ባሕርን ያጣንበት መንገድ ሕጋዊ ነው ወይስ ተፅዕኖ ነበረበት? በዚያ ሂደት ከመጋረጃ ጀርባ የሌሎች አካላት ሚና ምን ነበር?” የሚለውንም ማጤን እንደሚገባ ጠቁመዋል።

የባሕር በር ጥያቄ  አሁን መነሳቱ ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን ገልጸው፤ ከኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ባሻገር ለኢትዮጵያ ሰላም እና መረጋጋት ጭምር በእጅጉ አስፈላጊ ስለመሆኑም ነው የታሪክ ተመራማሪው ፕሮፌሰር አደም ካሚል የተናገሩት።

በቢታንያ ሲሳይ

#ebcdotstream #ethiopia #seaport #redsea