Search

ሁሉም ዜጋ ለብሔራዊ ጥቅም ዘብ መቆም አለበት

ረቡዕ ጥቅምት 05, 2018 36

ሁሉም ዜጋ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ዘብ መቆም አለበት ሲሉ በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ግንኙነት እና ዲፕሎማሲ መምህሩ አቶ ሙሉዓለም ኃ/ማሪያም ገለጹ።

አቶ ሙሉዓለም ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ጋር በነበራቸው ቆይታ፥ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ በተለያዩ ጊዜያት የምታከናውናቸው ተግባራት እንዳሉ አንስተዋል።

አክለውም፥ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ የመንግሥት ብቻ ሳይሆን የሁሉም ኢትዮጵያዊ አጀንዳ ስለመሆኑ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ያነሳችው የባሕር በር ጥያቄ የሀገሪቱ ብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህ ጥያቄ ዙሪያ ሁሉም ዜጋ በአንድነት መቆም እንዳለበት አመላክተዋል።

በሜሮን ንብረት

#ebcdotstream #ethiopia #seaport #nationalinterest