Search

በድህነት ውስጥ የተወለደው የኒውክሌር ህልም፦ ሩፑር

ዓርብ ጥቅምት 07, 2018 6313

"ከምኞት የማይዘል የድሀ ሀገር ህልምተብሎ የተተቸው ፕሮጀክት እውን የሆነበት ምስጢር

ከባንግላዴሽ ዋና ከተማ ዳካ በስተምዕራብ በሚገኘው የፓድማ ወንዝ ዳርቻ ላይ የተገነባው የሩፑር ኒውክሊየር ኃይል ማመንጫ እንደዋዛ የሚታይ ቀላል የኮንክሪት እና የብረት ክምር ብቻ አይደለም።

ሩፑር ኒውክሊየር ማመንጫ የባንግላዴሽ የድህነት ዘመን መቋጫ፣ የብሔራዊ ፅናት ምልክት እና ተስፋ መቁረጥን አልቀበልም ያለ የአንድ ሀገር የጀግንነት መዝገብ ነው።

ባንግላዴሽ የኒውክሊየር ኃይል ማመንጫ መገንባት ካልቻለች የምታስበውን ዕድገት ማሳካት እንደማትችል የተገነዘቡት መሪዎች፣ ገና 1961 የኒውክሊየርይል ማመንጫ ሊኖር እንደሚገባ የፕሮጀክት ውጥን ሃሳብ ነበራቸው። 

በእርግጥ በዚህ ወቅት ስለኒውክሊየር ማውራት የሚያስታውሰው በሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ ጥቁር ጠባሳ ስለጣለው የኒውክሊየር ቦምብ ብቻ ስለነበር የተወገዘ ቃል ይመስል ነበር። 

ኒውክሊየር ሳይንስ በሰው ልጅ የምርምር ዘርፍ ውስጥ እጅግ ምጡቅ እና ተፈጥሯዊ የኃይል አማራጮች ላይ ብቻ የነበረውን አተያይ መቀየር የተቻለበት ነው። ይህን ቴክኖሎጂ ግን ለጥፋትም ለልማትም መጠቀም እንደሚቻል ሁሉ፣ በአንድ የታሪክ አጋጣሚ ይህን ቴክኖሎጂ ለክፋት በመጠቀም ብዙ መሥራት የሚቻልበትን ቴክኖሎጂ በጥርጣሬ ውስጥ  እንዲቆይ በር ከፍቷል። 

ይህም ሆኖ ግን ሳይንሱ እና ቴክኖሎጂው የገባቸው ሀገራት ከኒውክሊየር የጸዳ ዓለም እንፍጠር እያሉ ቢሰብኩም፤ እነሱ ግን የኒውክሊየርይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ከመሥራት አልቦዘኑም። 

ይህን የተረዱት ባንግላዴሾች ቀድሞ የተጀመረውን የኒውክሊየር ሃሳብ በማጠናከር 1963 በሰሜን ምዕራብ ዳሃካ በጋንጀስ ወንዝ አካባቢ የግንባታ ቦታ በመምረጥ ፕርጀክቱ በመንግሥትም እውቅና የተሰጠው ሆነ። 

በወቅቱ ይህች ሀገር የኒውክሊየር ኃይል ማመንጫ የመገንባት ፍላጎት እንጂ አቅም የላትም የሚሉ ድምጾች የሚሰሙባት ብትሆንም፤ ነገን አሻግረው የተመለከቱት ግን በውስጥም በውጭም የነበረውን ጩኸት በብልሃት በማለፍ ሥራቸውን ከመሥራት አልተዘናጉም። 

ባንግላዴሾች ከነጻነታቸው በኋላ 125 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ የሚያመነጭ የኒውክሊየር ጣቢያ ለመገንባት 1980 የጸደቀ ቢሆንም፤ ይህን ዕቅድ እንደገና በመከለስ 1990 መንግሥት በሩፑር የኒውክሊየር ኃይል የመገንባት ጥብቅ ፍላጎቱን በመግለጽ ጉዳዩ ወደፊት እንዲመጣ አድርገዋል። 

እዚህ ላይ ባንግላዴሽ የኒውክሊየር ግንባታ ላይ ያላት ጽኑ ፍላጎት ማየሉን የተመለከቱ ከምዕራብ ጫና ከምስራቅ ደግሞ እኛ እንስራው የሚል ፍላጎታቸውን የገለጹበት ወቅትም ሆኗል። እናም 2001 የኒውክሊየር ኃይል የድርጊት ዕቅድ ይፋ አደረገች።

2005 ደግሞ ሩስያ፣ ደቡብ ኮርያ እና ቻይና ነገሩ ስለገባቸው ፕሮጀክቱን ለመገንባት ቀደም ብለው ፍላጎታቸውን ያሳዩ ሀገራት ሲሆኑ፤ ባንግላዲሽም ከቻይና ጋር የኒውክሊየር ትብብር ስምምነት በመፈራረም ጉዳዩ ወደ ተግባር መግባቱን ለዓለም ለመግለጠጥ ተንደርድረዋል። 

ባንግላዴሽ የሩፑር የኒውክሊየርይል ማመንጫን  ለመገንባት በወሰነችበት ወቅት ይህን ግዙፍ ፕሮጀክት ለመገንባት የሚያበቃ አቅም ላይ አልነበረችም የሚለው አንዱ የተቃውሞ ድምጽ ነበረ። 

በአውሮፓውያኑ 2011 ባንግላዴሽ ከሩሲያ ጋር የሩፑር ኒውክሊየር ፕሮጀክት ስምምነት በፈረመችበት ወቅት ሀገሪቱ ከፍተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ኢኮኖሚዋን ለማሳደግ የምትሞክርበት ወቅት ቢሆንም፤ 40 በመቶ በላይ የሚሆነው ህዝብ ከድህነት ወለል በታች ይኖር ነበር።

የኢንዱስትሪዎች መስፋፋት እና ከድህነት ለመውጣት የመሻት ሥራ በኤሌክትሪክ ኃይል ወደኋላ ሊመለስ እንደሚችል የገባቸው የወቅቱ መሪዎች፣ በአንድ በኩል መብራት እንኳን ማግኘት ያልቻሉ ዜጎችን ፍላጎት ለማሟላት፣ በሌላ በኩል ደግሞ የተከፈቱት ፋብሪካዎች እንዳይቋረጡ የሚያስችል ሥራ ላይ እጃቸውን አላቆሙም። 

እናም በእንደዚህይነት የገንዘብና የሀብት እጥረት ውስጥ ሆኖ 12.65 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ ፕሮጀክት መጀመር ጥበብን ብቻ ሳይሆን ድፍረትን የሚጠይቅ ውሳኔ ነበር። 

የባንግላዴሽ ኒውክሊየር የመገንባት ሀሳብ እንደተሰማ ተቺዎች "ከምኞት የማይዘል የድሀ ሀገር ህልም" በማለት አጣጥለው ነበር። ይሁን እንጂ  የባንግላዴሽ መሪዎች መጪውን ዘመን ተመልክተው ዘላቂ እና ርካሽ የኃይል ምንጭ ከሌለ ሀገሪቱ ከድህነት ለመውጣትም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለመወዳደር እንደማትችል በማመናቸው፣ ሀገሪቱን ለዘመናት ከነበረችበት የጨለማ ታሪክ ያወጣል ያሉትን ታላቁን የሩፑር ፕሮጀክት አስጀመሩ። 

በዚህ ውሳኔ መሰረት ባንግላዴሽ ይህን በሀገሪቱ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ታላቅ ፕሮጀክት ስትጀምር በወቅቱ የነበረው የባንግላዴሽ አጠቃላይ ዓመታዊ የሀገር ውስጥ ምርት 100 ቢሊዮን ዶላር ብዙም የማይበልጥ ነበር። ሆኖም ውሳኔው የሀብታምነት ሳይሆን የረጅም ጊዜ የህልውና ጥያቄ ነበርና የነበሩበትን ሁኔታ ወደጎን በማድረግ በይቻላል መንፈስ ታላቁን ፕሮጀክት እውን ለማድረግ መረባረብ ጀመሩ። 

በዚህ መልኩ የተጀመረው የባንግላዴሽ የሩፑር የኒውክሊየርይል ማመንጫ ግንባታ ያጋጠመው ታዲያ የገንዘብ እጥረት ብቻ አልነበረም። በተለይ የፕሮጀክቱ ተጀምሮ ግማሽ ላይ እንደደረሰ በዓለም አቀፍ ደረጃ አጋጥሞ የነበረው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ፕሮጀክቱን ለመጨረስ ፈተና ሆነ። በአካባቢው የተፈጠረው ጂኦ ፖለቲካዊ ውጥረት እና  የተፈጥሮ አደጋ ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት ችግር ውስጥ እንዲወድቅ አድርጓል። 

ሆኖም እነዚህ ተግዳሮቶች ፕሮጀክቱን ማዘግየት እንጂ ማስቆም አልቻሉምና  ባንግላዴሾች ያጋጠሟቸውን የፋይናንስ፣ የፖለቲካ እና የቴክኒክ ችግሮችን ተቋቁመው በድህነት ወቅት ያለሙትን ህልም እውን ለማድረግ ጠንክረው መሥራታቸውን ቀጠሉ። 

በዚህ ሁኔታ በብዙ መሰናክሎች ውስጥ ሲገነባ የቆየው እና የዓመታት የብርቱ ጥረት ውጤት የሆነው የሩፑር የኒውክሊየር ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትራው እየተጠናቀቀ የሚገኝ ሲሆን፤ በዚህመት መጨረሻ ላይ እንደሚጀምር ይጠበቃል። በቅርቡም ባንግላዴሽ ከኒውክሊየርይል የምታመነጭ 33ኛዋ ሀገር ሆና ትመዘገባለች። 

ይህ የባንግላዴሽ ተሞክሮ ከኃይል ማመንጨት በላይ ነው፤ የዚህች ሀገር ተሞክሮ ትልቅ ህልምና ራዕይ የሰነቁና ይህንንም ለመተግበር የሚያስቡ ሀገራት ፈተናዎችን አልፈው ካሰቡበት ደረጃ መድረስ እንደሚችሉ ማሳያ ነው። 

በዋሲሁን ተስፋዬ