ፓኪስታን የ15 ቀኑ የተኩስ አቁም ስምምነት ከማብቃቱ በፊት በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረግ ሁለተኛ ዙር ድርድር በኢስላማባድ ለማስተናገድ ሐሳብ ማቅረቧን አሶሺየትድ ፕሬስ ዘግቧል።
የዜና ወኪሉ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ሁለት የፓኪስታን ባለሥልጣናትን ጠቅሶ እንደዘገበው፣ ሀገሪቱ ይህንን ጥያቄ ያቀረበችው ውጥረቱን በዘላቂነት ለመቀነስ ካላት ፍላጎት በመነሣት ነው።
የሐሳቡ ተግባራዊነት የሚወሰነው ተደራዳሪ ወገኖቹ ሌላ የተለየ ቦታ እንዲመቻችላቸው የሚጠይቁ መሆን አለመሆኑ ላይ እንደሆነ ባለሥልጣናቱ መግለጻቸው ተጠቁሟል።
በኢራን እና በአሜሪካ መካከል ሁለተኛው ዙር ድርድር በቅርብ ቀናት ውስጥ፣ ምናልባትም ሐሙስ ዕለት ሊደረግ እንደሚችል ተዘግቧል።