Search

46 ዓመታትን የፈጀው የበረሃ ላይ ትግል፤ የቻይናው ታላቁ አረንጓዴ ግንብ አስገራሚ ስኬት

ማክሰኞ ሐምሌ 21, 2018 56

በቅርቡ በሺንጂያንግ ግዛት በተደረገ ጉዞ፣ በቅርብ ጊዜ ክፍት በረሃ በነበሩ አካባቢዎች አዳዲስ የተተከሉ እና ገና ያልጎመሩ ዛፎች አውራ ጎዳናዎችን አጅበው መመልከት የተለመደ ትዕይንት ሆኗል። ከቱርፓን እስከ ኡሩምኪ ዳርቻዎች የሚታየው ይሄው ተመሳሳይ ገጽታ፣ ይህ ምንድን ነው? እና ምን ያህል ጊዜ ፈጅቷል? የሚል ጥያቄን በውስጥ ያጭራል። ምላሹ አሁን በመንገዱ ላይ ከሚያልፉት አብዛኛዎቹ ሰዎች ዕድሜ የሚበልጥ ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑ ነው።

የፕሮጀክቱ ዋና ሀሳብ ቀላል ቢሆንም፣ አፈጻጸሙ ግን አሥርተ ዓመታትን የወሰደ ነው። በሰዎች የተተከሉት የዛፍ መስመሮች ንፋስን በመግታት የጎቢ በረሃ መስፋፋትን የሚከላከሉ ሲሆን፣ ለአካባቢው ማኅበረሰብም የጣውላ ምንጭ ሆነው ያገለግላሉ።

1978 የተጀመረው ይህ ፕሮግራም እስከ 2050 . ድረስ የሚቀጥል ሲሆን፣ ሲጠናቀቅ ወደ 3000 ማይልስ ርዝመት እና 88 ሚሊዮን ኤከር የደን ሽፋን ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል። ቻይና በዓለም ላይ ካሉ ሀገራት በበረሃማነት ስድስተኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ ሲሆን፣ ይህንኑ አስከፊ የበረሃ መስፋፋት ለመቀልበስ "ታላቁ አረንጓዴ ግንብ" እየተገነባ ይገኛል።

1978 . ጀምሮ ሠራተኞች የጎቢን እና የታክላማካንን በረሃዎች ወደፊት መገስገስ ለመግታት 66 ቢሊዮን የሚገመቱ ዛፎችን ተክለዋል። 2024 የፊንላንድን የሚያህል ስፋት ያለውን የታክላማካን በረሃ የሚከበው 3044 ኪሎ ሜትር አረንጓዴ ቀበቶ የመጨረሻው ክፍተት ተዘግቷል።

የቻይና የሳይንስ አካዳሚ ተመራማሪ የሆኑት ጂያኦጁን እንዳስገነዘቡት፣ 2000  ወዲህ የቻይና በረሃማ መሬት 10 በመቶ ሲቀንስ፣ እጅግ የከፋ በረሃማነት የታየባቸው አካባቢዎች ደግሞ 40 በመቶ በላይ ቀንሰዋል።

በፕሮግራሙ በተሸፈኑ አካባቢዎች የነበረው የደን ሽፋን 1978 ከነበረው 5 በመቶ 2022 ወደ 14 በመቶ ማደጉ የፕሮጀክቱን ስኬት በተጨባጭ ያሳያል። ዛፎች በፍጥነት እያደጉ በመሆናቸው፣ በታክላማካን ዙሪያ ያለው አረንጓዴ ቀበቶ በረሃው ከሚለቀው በላይ ካርቦን በመምጠጥ ላይ ይገኛል።

ታሪኩን ይበልጥ ሳቢ የሚያደርገው ዛፎቹ ከጸደቁ በኋላ የተፈጠረው ክስተት ነው። በኩቡኪ በረሃ፣ ሠራተኞች ዛፍ በመትከል ብቻ አላቆሙም፤ በተረጋጋው አሸዋ ላይ የፀሐይ ኃይል ማመንጫዎችን ገንብተዋል። እነዚህ ማመንጫዎች ለዋናው መረብ ኃይል ከማመንጨት ባሻገር፣ ጥላ በመፍጠር የውሃ ትነትን ስለሚቀንሱ ከስራቸው ቁጥቋጦዎችና ሳሮች እንዲበቅሉ አስችለዋል።

የኩቡኪ ፕሮጀክት 500 ቢሊዮን ዩዋን በላይ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያስገኘ ሲሆን፣ 100 ሺህ በላይ የአካባቢውን ነዋሪዎች ከድህነት በማውጣት ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሥራ ዕድሎችን ፈጥሯል።

አሁን ላይ የአካባቢው ነዋሪዎች የፀሐይ ፓነሎቹን በመንከባከብ፣ ከሥራቸው ሰብሎችን በማምረት እና በአዲሱ የሳር ምድር ላይ እንስሳትን በማርባት ላይ ሲሆኑ፣ ፀረ-በረሃማነት ትግሉ እና የገቢ ምንጭ መፍጠር አብረው ሊሄዱ እንደሚችሉ በተግባር አሳይተዋል።

የቻይና አካሄድ ንፋስን ለመስበር እና ችግኞች ፀድቀው ስር እንዲሰድዱ የደረቁ ዕፅዋትን በቼዝ ሰሌዳ ቅርጽ በማዘጋጀት ላይ የተመሰረተ ቀላል ግን እጅግ ውጤታማ ዘዴ ነው። 2018 ጀምሮ ቻይናውያን ተመራማሪዎችና መሐንዲሶች በሳህል ቀጠና መሬትን መልሶ ለማልማት 2007 ከተጀመረው የአፍሪካ ታላቁ አረንጓዴ ግንብ ተነሳሽነት አባል ከሆኑት ኢትዮጵያ፣ ሞሪታንያ እና ናይጄሪያ ጋር በመተባበር ላይ ይገኛሉ።

ይህ ትብብር የሳተላይት ክትትልን እና የርቀት ዳሳሾችን ጭምር ያካተተ ሲሆን፣ አፍሪካውያን አጋሮች የመሬት መራቆትን ቻይና የራሷን የከለላ ቀበቶ በምትከታተልበት መንገድ በቅጽበት መከታተል እንዲችሉ አድርጓል።

ይሁን እንጂ ፕሮጀክቱ ገና አላለቀም፤ ቻይና በሚቀጥሉት 25 ዓመታት ውስጥ ተጨማሪ 34 ቢሊዮን ዛፎችን ለመትከል አቅዳለች። ይህ ማለት 1980ዎቹ ፕሮጀክቱን የጀመሩት ሠራተኞች አሁን ልጆቻቸው እና የልጅ ልጆቻቸው በዚያው በረሃ ላይ ሥራውን ሲያስቀጥሉ እያዩ ነው።

እንደ ቻይና ፎከስ ዘገባ ተፈጥሮን የመታደግ ሥራ ቀስ ብሎ የሚጓዝ፣ ተደጋጋሚ እና አሥርተ ዓመታትን የሚጠይቅ ቢሆንም፣ በረሃው መስፋፋቱን እስኪያቆም ድረስ በየጊዜው በአሸዋ ላይ አንድ ትንሽ ጉድጓድ በመቆፈር የሚገነባ ዘላቂ የድል ጉዞ ነው።

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: