የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ከአቡ ዳቢው አልጋ ወራሽ መሐመድ ቢን ዛይድ ጋር ባደረጉት ውይይት በመካከለኛው ምሥራቅ ሰላም እና መረጋጋትን ለማጠናከር የሚያስችል ባለ አራት ነጥብ የውሳኔ ሐሳብ ማቅረባቸውን ሺንዋ ዘግቧል።
የውሳኔ ሐሳቡ በሰላም አብሮ መኖር፣ ብሔራዊ ሉዓላዊነት እና ዓለም አቀፍ የሕግ የበላይነት መርሆዎች ላይ ትኩረት የሚያደርግ ሲሆን፣ ለደኅንነት እና የልማት ቅንጅት አስፈላጊነትም አፅንዖት ይሰጣል።
ፕሬዚዳንቱ፣ “በመካከለኛው ምሥራቅ የሚገኙ የባሕረ ሰላጤው ሀገራት ሉዓላዊነት፣ ደኅንነት እና የግዛት አንድነት በቅንነት ሊከበር ይገባል” ማለታቸውን የቻይና የቴሌቪዥን ጣቢያ (CCTV) ዘግቧል።