Search

አሜሪካ እና ኢራን ለውይይት ፊት ለፊት የሚገናኙበት ዕድል አለ - ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ

ዓርብ ሚያዝያ 09, 2018 74

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ አሜሪካ እና ኢራን በሳምንቱ መጨረሻ ፊት ለፊት የሚገናኙበት ዕድል መኖሩን ገለጹ።

ትራምፕ በዋይት ሃውስ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ ከኢራን ጋር ስምምነት ላይ ለመድረስ ሰፊ ዕድል መኖሩንና ይህም ስምምነት ኢራን የኒውክሌር መሣሪያ እንዳይኖራት የሚያረጋግጥ መሆኑን ተናግረዋል።

ኢራን አሁን ላይ ስምምነት ለማድረግ ፍላጎት እንዳላትና ከሁለት ወራት በፊት ያልነበሩ አዳዲስ አማራጮችን ለማቅረብ ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል።

ከዚህ ቀደም ይነገር የነበረውን የ20 ዓመት የኑክሌር እገዳ የጊዜ ገደብ ትራምፕ ውድቅ በማድረግ፣ ስምምነቱ ከዚያ በላይ የሚዘልቅ ጠንካራ መሆኑን አብራርተዋል።

ትራምፕ ትላንት በሰጡት አስተያየት የአሜሪካ-እስራኤል እና የኢራን ግጭት "ሊያበቃ በጣም ተቃርቧል" ብለው ነበር።

#MiddleEast #USA #Iran #PeaceTalks #DonaldTrump