ነገ ሰኞ ለሚካሄደው የኢትዮጵያ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጥቂት ሰዓታት በቀሩበት በዚህ ወቅት፣ የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን በመሬት ላይ ያለውን ሂደት በንቃት የመታዘብ ሥራውን እያከናወነ ይገኛል።
የቡድኑ የመስክ ታዛቢዎች በተመደቡባቸው ልዩ ልዩ ወረዳዎችና አካባቢዎች በመሰማራት፣ ከአካባቢው ባለሥልጣናት፣ ከሲቪል ማኅበረሰብ አካላት እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶችን በማድረግ ላይ ናቸው።
ታዛቢዎቹ በታችኛው መዋቅር ያለውን የቅድመ ምርጫ ዝግጅት፣ የሂደቱን ሁሉን አቀፍነት እና አጠቃላይ የድምፅ አሰጣጥ ከባቢ ሁኔታን በመገምገም፣ ለታዛቢ ቡድኑ አጠቃላይ ከምርጫ በኋላ ትንተና መሠረት የሚሆኑ እውነተኛና ወቅታዊ መረጃዎችን በማሰባሰብ ላይ መሆናቸው ታውቋል።