የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሀሳብ አመንጪነት እና አስተባባሪነት ኢትዮያን ከበረሃማነት በመታደግ አረንጓዴ ገጽታዋን የመመለስ ትልቅ ራዕይ ሰንቆ የተጀመረ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።
በአረንጓዴ አሻራ ከ2011 እስከ 2018 ዓ.ም ባለፉት 8 ዓመታት ኢትዮያውያንን ከዳር እስከዳር በማስተባበር አስደናቂ የስኬት ታሪክ ተጽፏል።
የመርሀ ግብሩ ጅማሮ በ2011 ዓ.ም ሲከፈት ከ4 ቢሊዮን በላይ ችግኞች በመትከል የነገዋን አረንጓዴ ኢትዮጵያ መሰረት ጥሏል። በ2012 ዓ.ም "በመትከል ማንሰራራት" በሚል አገራዊ ስሜት ከ5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል።
በአረንጓዴ አሻራ ላይ የህዝቡ ተነሳሽነት ይበልጥ እያደገ መጥቶ በ2013 ዓ.ም “ኑ ኢትዮጵያን አረንጓዴ እናልብስ” በሚል መሪ ቃል ከ6.8 ቢሊዮን በላይ ችግኞች መሬት የነኩ ሲሆን፣ በ2014 ዓ.ም ደግሞ “አሻራችንን ለልጆቻችን” በሚል ራዕይ ከ7.2 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል።
የአረንጓዴ አሻራ ባህል በሕዝቡ ዘንድ ጠንካራ መሠረት እየያዘ መጥቶ በ2015 ዓ.ም “አሻራችን ለትውልዳችን፤ ለትውልድ እንስራ፤ ለኢትዮጵያ እንትከል” በሚል መሪ ሀሳብ ከ7.5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል።
በ2016 ዓ.ም ደግሞ ''የምትተክል ሀገር የሚያፀና ትውልድ'' በሚል መሪ ቃል በተመሳሳይ ከ7.5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የኢትዮያን ምድር አልብሰዋል።
ኢትዮያውያን አምና በ2017 ዓ.ም ይህ ቁጥር የአገራችንን አልፎ ዓለም አቀፍ ክብረወሰን ጭምር ሰብሮ ከ8 ቢሊዮን በላይ ችግኞች በመትከል ማሳካት ተችሏል።
የዘንድሮው የ2018 ዓ.ም መርሀ ግብርም ይህንኑ የዕድገት ጉዞ በማስቀጠል ከ8 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ይተከላሉ ተብሎ ታቅዷል።
ይህ የስምንት ዓመታት የአረንጓዴ አሻራ ጉዞ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ትግል ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየ አኩሪ አገራዊ ድል ነው።