መንግሥት ለታጠቁ ኀይሎች በተደጋጋሚ የሰላም አማራጮችን ሲያቀርብ መቆየቱን ተከትሎ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ብቻ 3 ሺህ 162 የታጠቁ ኀይሎች የሰላምን አማራጭ ተቀብለው ትጥቃቸውን መፍታታቸውን ዞኑ አስታውቋል።



የሰሜን ሸዋ ዞን ሰላም እና ጸጥታ መምሪያ ኀላፊ ይደሰቱ ክፈተው እንደገለፁት በ2018 በጀት ዓመት ብቻ ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በሺህዎች የሚቆጠሩ ታጣቂዎች በዞኑ የሰላም አማራጭን ተቀብለዋል።
እነዚህም ከተሀድሶ ኮሚሽን ጋር በመቀናጀት በሦሥት ዙር የመልሶ ማቋቋም ሥልጠና አግኝተው ወደ ማኅበረሰቡ መቀላቀላቸውን አንስተዋል።
አሁን ላይም በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢንዱስትሪ እና በግብርናው ዘርፍ የሥራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው የዘገበው አሚኮ ነው።