Search

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሊዮን የመጀመሪያ በረራ አደረገ

ሓሙስ ሰኔ 25, 2018 82

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ታሪካዊቷና ውቧ ከተማ ሊዮን የተጀመረው አዲሱ የበረራ መስመር መዳረሻውን ሲያደርግ ደማቅና ሞቅ ያለ አቀባበል ተደርጎለታል።

ይህ አዲስ በረራ በይፋ መጀመሩን ተከትሎ ወደ ከተማዋ ያቀናው የመጀመሪያው በረራ በድምቀት ተስተናግዷል።

ወደ ፈረንሳይዋ ሊዮን ከተማ የሚደረገው ይህ አዲሱ በረራ በደማቅ ሁኔታ መጀመሩ፣ አየር መንገዱ በአውሮፓ ያለውን ተደራሽነት ይበልጥ የሚያሰፋና የደንበኞችን የጉዞ አማራጭ የሚያሰፋ ስኬት ነው።