Search

የ76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እያካሄዱ ነው

እሑድ ነሐሴ 17, 2018 91

76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ ተሳታፊዎች የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና የእግር ጉዞ በኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት መንገዶች እያካሄዱ ነው።

ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 . በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት  በአዲስ አበባ በሚካሄደው ስብሰባ ላይ ለመካፈል ከአህጉሪቱ 47 አባል ሀገራት የተወጣጡ የጤናና የፋይናንስ ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሕዝብ ጤና ባለሙያዎችና የልማት አጋሮችን ጨምሮ 800 በላይ ተሳታፊዎች ናቸው ከዓድዋ መታሰቢያ ጀምሮ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና የእግር ጉዞ  እያካሄዱ የሚገኙት።

የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ እና የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ዳይሬክተር ፕሮፌሰር  ጃናቢ የአካል ብቃት እንቅስቃሴውን እና የእግር ጉዞውን አስጀምረዋል።

ሚኒስትሯ በዚህ ወቅት፣ በጤናው ዘርፍ የሚፈለገውን ግብ ለማሳካት ከንግግር ያለፈ ቁርጠኝነት አስፈላጊ በመሆኑ ኢትዮጵያ ቃልን ወደ ተግባር እየቀየረች መሆኑን አብራርተዋል።

በአካል ብቃት እንቅስቃሴው እና የእግር ጉዞው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማኅበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ / ወርቅሰሙ ማሞን ጨምሮ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር ስለሺ ስህን እና ታዋቂ ኤሌቶች ተገኝተዋል። 

የቀጣናው የውሳኔ ሰጪዎች ይፋዊውን ስብሰባ ከመጀመራቸው አስቀድሞ፣ ውሳኔዎቻቸውን በተግባር ለማስደገፍ “Walk the Talk ቃልን በተግባርበሚል በመሪ ሐሳብ የኮሪደር ልማት በተከናወነባቸው እና ለጤናና ለአካል ብቃት እንቅስቃሴ ምቹ በሆኑ ጎዳናዎች የእግር ጉዞና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እያደረጉ ነው።

በብሩክ ተስፋዬ

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: