Search

በጌዴኦ ዞን ራጴ ወረዳ በደረሰ የመሬት ናዳ የ9 ሰዎች ሕይወት አለፈ

ሓሙስ ነሐሴ 22, 2017 374

በጌዴኦ ዞን ራጴ ወረዳ በጫራቃ እና በሀሮ ቀበሌ ትላንት ከምሽቱ 5 ሰዓት አከባቢ የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ በደረሰ የመሬት ናዳ እስካሁን 9 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል። 

የጌዴኦ ዞን ፖሊስ ዋና አዛዥ ኢንስፔክተር ብሩ ማርቆስ ለኢቢሲ እንደገለጹት፤ ትላንት ማምሻውን በረዶ ቀላቅሎ የጣለው ከባድ ዝናብ ለአደጋው ምክንያት ሆኗል። 

በመሬት ናዳው ከሞቱ 9 ሰዎች መካከል 6 ወንዶች ሲሆኑ የተቀሩት ሴቶች መሆናቸውንም አመላክተዋል።

አካባቢው ለናዳ አደጋ ተጋላጭ በመሆኑ ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባልም ተብሏል።

በተመስገን ተስፋዬ