Search

ነገ በአዲስ አበባ ለተሽከርካሪዎች ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ሆኑ

ዓርብ የካቲት 27, 2018 114

ነገ ቅዳሜ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ የሚከናወነውን ታላቁን የኢፍጣር መርኃ ግብር ምክንያት በማድረግ፣ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።
በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ የሚካሄደውን ይህንን መርሐ-ግብር ተከትሎ ከቀኑ 5፡00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ የሚከተሉት መንገዶች ዝግ ይደረጋሉ፦
👉 ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል ቤተክርስቲያን
👉 ከወሎ ሰፈር ወደ መስቀል አደባባይ ኦሎምፒያ
👉ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ አሽከርካሪዎች ለከባድ መኪናዎች አጎና ሲኒማ፤ ለሌሎች ተሽከርካሪዎች ጥላሁን አደባባይ ጋር ዝግ የሚደረግ ይሆናል፡፡
👉 ከጦር ኃይሎች በሜክሲኮ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች በተለምዶ አጠራሩ ክቡ ባንክ አካባቢ
👉ከፒያሳ በቸርችል ጎዳና ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ሐራምቤ መብራት ላይ
👉 ከ4 ኪሎ በውጭ ጉዳይ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ብሔራዊ ቤተ መንግስት መስቀለኛው ላይ
👉 ከአዋሬ አካባቢ በካሳንቺስ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ኢንተርኮንትኔታል አካባቢ ከቀኑ 5፡00 ሰዓት ጀምሮ የኢፍጧር ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅበት ሰዓት ድረስ ዝግ ይደረጋሉ።
በተጠቀሱት መንገዶች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ሆነ ለረጅም ሰዓት አቁሞ መሄድ በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን ፖሊስ አሳስቧል።
ኅብረተሰቡ ለፀጥታ ሥጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በነጻ የጥሪ መስመሮች 990፣ 991፣ 987፣ 816 እንዲሁም በ011-1-26-43-59፣ 011-5-52-63-02/03፣ 011-5-52-40-77፣ 011-5-54-36-78 እና 011-5-54-36-81 በመደወል ወይም በEFPApp መተግበሪያ ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ ቀርቧል።