Search

ፅናት የሚመነጨው ከሀገር ፍቅር ነው፦ የመከላከያ ሚኒስቴር አመራሮች

ቅዳሜ ጳጉሜን 01, 2017 50

ፅናት የሚመነጨው ከሀገር ፍቅር ነው ሲሉ የመከላከያ ሚኒስቴር አመራሮች ገለጹ።

"ሀገር ከሌለ ማንም ሰው ክብር የለውም" ያሉት የኢ..ዴ. መከላከያ ሚኒስቴርልዩ ዘመቻዎች አዛዥ / ሹማ አብደታ፤ ሀገርን መጠበቅ ደግሞ ፅናትን ይጠይቃል ሲሉ ገልጸዋል።

ጀግኖች አባቶቻችን በባዶ እግራቸው ተጉዘውድዋ ላይ ያን ታላቅ ድል ያስመዘገቡት ፅናት ስለነበራቸው ነው ብለዋል ሌ/ ሹማ ከኢቲቪ ጋር በነበራቸው ቆይታ።

ኢትዮጵያ ያሏት ጠባቂዎች ህዝቧ፣ ወታደሩ እና ፖሊስ ሠራዊቱ እንደሆኑ የጠቀሱት የኢ..ዴ. መከላከያ ሚኒስቴር ዋር ኮሌጅ ዋና አዛዥ / ቡልቲ ታደሰ በበኩላቸው፥ ወታደር እና ፖሊስ በፅናት ሀገራቸውን እንዲጠብቁ ሀገር ወዳድ መሆን አለባቸው ብለዋል።

ሀገሩን የሚወድ በፅናት ይኖራል፤ ለሀገሩ መከፈል ያለበትን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚደርስ ዋጋም በፅናት ይከፍላል ነው ያሉት።

ኢትዮጵያ በተለያዩ ጊዜያት ከውጭም ከውስጥም ችግሮች በገጠሟት ጊዜ ወታደሮቿ በቁርጠኝነት፣ በፅናት እና በአይበገሬነት የሀገራቸውን ክብር እና ሉዓላዊነት ጠብቀዋል ብለዋል።

በሜሮን ንብረት

#EBCdotstream #ETV #Ethiopia #ENDF #resilience #የፅናትቀን