Search

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የመልካ ቃሊቲ የሎጂስቲክስ ማዕከልን መርቀው ከፈቱ

ቅዳሜ ጳጉሜን 01, 2017 65

የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በዛሬው ዕለት የመልካ ቃሊቲ የሎጂስቲክስ ማዕከልን ዛሬ መርቀው ከፍተዋል።

ማዕከሉ ደረጃውን የጠበቀ የውስጥ ለውስጥ አስፓልት መንገድ፣ የኳስ ሜዳ፣ የመዝናኛ ክበብ እና ሌሎች አስፈላጊ መሠረተ ልማቶች የተሟሉለት ነው።

የመከላከያ ሎጂስቲክስ ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል አብዱራህማን እስማኤል በምረቃው ወቅት፥ ማዕከሉ የሎጂስቲክስ አቅርቦት ማከማቻ መሆኑን አስረድተዋል።

ማዕከሉ ከዚህ ቀደም ለስራ ምቹ እንዳልነበረ አስታውሰው፤ አሁን በአመራሩ ቁርጠኝነት ፅዱና ለሥራ ምቹ አካባቢ መፍጠር መቻሉን ገልጸዋል።

ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በተጨማሪ የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጀኔራል አበባው ታደሰ፣ ጀነራል መኮንኖች እንዲሁም የዕዝ፣ የኮር እናክፍለጦር አመራሮች በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተዋል።

#EBCdotstream #DefenseForce #LogisticsCenter