Search

የኅብር ቀን በሰመራ ከተማ እየተከበረ ይገኛል

እሑድ ጳጉሜን 02, 2017 68

የኅብር ቀን በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ "ብዝሃነት የኢትዮጵያ ጌጥ" በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ መርሃ-ግብሮች እየተከበረ ይገኛል።

የሰመራ ከተማ ነዋሪዎች ፣ ወጣቶች ፣ የመንግሥት ሰራተኞች እና ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች በተገኙበት የመንገድ ላይ ትርዒቶች ቀርበዋል።

 



ኢትዮጵያውያን በዐድዋ ድል፣ በታላቁ የሕዳሴ ግድብ እና በተለያዩ የልማት መስኮች ላይ ያሳዩትን ሕብረት የሚያወሱ ሁነቶችም ተካሂደዋል።

 



የኅብር ቀንን አስመልክቶ ለአቅመ ደካሞች የማዕድ ማጋራት መርሃ-ግብር ተከናውኗል።

 

 



#EBC #ebcdotstream #Unity #Afar

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ

ተያያዥ ዜናዎች: