Search

አዲስ-መሶብ በአዲስ ዓመት ለነዋሪዎች የቀረበ ገፀ በረከት ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ረቡዕ ጳጉሜን 05, 2017 70

የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓቱን የጠበቀ እና ቀልጣፋ እንዲሆን በቁርጠኝነት መስራታችንን ቀጥለናል ሲሉ የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታወቁ።

ዛሬ ጠቅላይ ሚንስትር  ዐቢይ አሕመድ (/ር) በተገኙበት "አዲስ መሶብ "የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ሥራ አስጀምረናል ብለዋል ከንቲባዋ።

በአዲሱ ዓመት ዋዜማ አዲስ-መሶብን እነሆ ገፀ በረከት ብለናል ሲሉ ከንቲባ አዳነች በማኅበራዊ የትስስር ገፃቸው አስፍረዋል።

13 ተቋማት 107 የከተማ አስተዳደር አገልግሎቶችን የሚሰጠው አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል የነዋዎቻችን እንግልት የሚቀንስ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት አዲስ ብስራት ይዘን መጥተናል ብለዋል።

በአዲሱ ዓመት በብዙ ብርታት እና ትጋት ልናገለግላችሁ ቆመናል ሲሉምም ገልጸዋል።

 

#EBC #ebcdotstream #Addis Abvaba #Mesob