Search

ሕዳሴ ግድብን አጠናቀን አዲሱን ዘመን መቀበላችን ደስታችንን እጥፍ አድርጎታል - ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሓሙስ መስከረም 01, 2018 76

በዘርፈ ብዙ ድሎች ደምቀን ለምናከብረው የ2018 አዲስ ዓመት እንኳን በሰላምና በጤና አደረሳችሁ ሲሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መልዕክት አስተላልፈዋል።

አቶ ደስታ በመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክታቸው፥ የህብረታችንን ጥንካሬ ያስመሰከርንበትንታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታን አጠናቀን እና አስመርቀንሀሴት ውስጥ ሆነን አዲሱን ዘመን መቀበላችን ደስታችንን እጥፍ ድርብ አድርጎታል ብለዋል።

ግድቡ ለአንድ ዓላማ በጋራ መሰለፍ ወደ ታለመ መዳረሻና ግብ የሚያደርሰን ድልድይ መሆኑን አሳይቶናልና የሀገራችን የዕድገት ልዕልና የሚረጋግጥበት ለሆነው ህብረታችን እና አድነታችን ልዩ ክብር ልንሰጠው ይገባል ብለዋል።

አዲሱ ዓመትሌሎች ታላላቅ ፕሮጀክቶች ግንባታን የምንጀምርበት እንዲሁም የጀመርናቸውን የምናፋጥንበት እና የምናስመርቅበት ይሆናል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ለዚህ ስኬት ሁላችንም ውድና መተኪያ የሌላትን ሀገራችንን በታማኝነትና በትጋት ማገልገል ይገባናል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

#EBCdotstream #Ethiopia #NewYear #EthiopianNewYear #2018EC