Search

የኢትዮጵያ ሬዲዮ የ90 ዓመት ጉዞ - በነገው የአዲስ ቀን የሀገር ጉዳይ

ሓሙስ መስከረም 01, 2018 176

በነገው የአዲስ ቀን የዜና መሰናዶ የሀገር ጉዳይ በኢትዮጵያ የሚዲያ ታሪክ ውስጥ የበኩር ድምፅ የሆነውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሬዲዮን ጉዞ እንዳስሳለን።
የሀገሪቱን ታሪኮች ለዘመናት ሰንዶ ያስቀመጠው አንጋፋው የሬዲዮ ጣቢያ መስከረም 2 ቀን 2018 ዓ.ም ስርጭት ከጀመረ ድፍን 90 ዓመት ይሆነዋል።
ኢቢሲ 90 ዓመታትን በብሔራዊ ሬዲዮ ፣ 60 ዓመታት በቴሌቪዥን እንዲሁም 25 ዓመታትን ደግሞ በኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ያስቆጠረ አንጋፋ ተቋም ነው።
አዲስ ቀን የዜና መሰናዶ ይህንን የሀገር ጉዳይ ጨምሮ ሌሎች ጥንቅሮችን አካቶ ነገ ከጠዋቱ 1:00 እስከ 3:00 ሰዓት ከነፃነት ፍቅሩ እና ከአብዮት ይግዛው ጋር ይጠብቃችኋል።
አዲስ ቀን!