Search

ሕዳሴ ግድብ ቀጣናዊ ትስስርን በማጠናከር ሌሎች ሀገራትን ጭምር ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው - በኢትዮጵያ የጀርመን ምክትል አምባሳደር

ዓርብ መስከረም 02, 2018 65

ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስርን በማጠናከር ሌሎች የአፍሪካ ሀገራትን ጭምር ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው በኢትዮጵያ የጀርመን ምክትል አምባሳደር ፈርዲናንድ ፎን ቫሄ (/) ገለጹ።

ከግድቡ ምረቃ ጋር በተያያዘኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት ምክትል አምባሳደሩ፥ ግድቡ ከፍተኛ የኤሌትሪክይል የማመንጨት አቅም ያለው መሆኑን ገልጸው፤ ጎረቤቶቿን ጨምሮ የአፍሪካ ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር ከሠሩ ተጠቃሚ መሆን እንደሚችሉ ተናግረዋል።

ታላቁሕዳሴ ግድብ በኢትዮጵያውያን ትብብር እውን መሆኑን አውቃለሁ ያሉት ምክትል አምባሳደሩ፤ የግድቡ ግንባታ ተጠናቅቆ ለምረቃ መብቃቱ የሚያኮራ ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ የተከናወኑ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ሀገሪቱን ለውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት የተመቸች እንዳደረጓትም ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ የካርበን ልቀትን ለመቀነስ እና የታዳሽይል አጠቃቀምን ለማስፋት የሚከናወኑራዎችን መመልከታቸውን ገልጸው፤ ይህም የሚበረታታ ተግባር ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያና ጀርመን በፀሐይና በሌሎች ታዳሽ የኃይል አማራጮች ላይ በጋራ ጥናትና ምርምር እየሠሩ እንደሚገኙም ምክትል አምባሳደሩ አንስተዋል።

#Ethiopia #GERD #Inauguration