Search

ግዙፉ ሕዳሴ ግድብ በራስ አቅም መገንባቱ በአፍሪካ ትልቅ መነሳሳትን ፈጥሯል

ዓርብ መስከረም 02, 2018 27

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለአፍሪካውያን ጭምር ኩራት መሆኑን የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ዜጎች ገለጹ።

በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚጠቀሱ 10 ታላላቅ ግድቦች አንዱ የሆነው ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በኢትዮጵያ በራስ አቅም መገንባቱም በአህጉሪቱ ትልቅ መነሳሳትን የፈጠረ ስለመሆኑ ተናግረዋል።

በኢንቴቤለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ (ኡጋንዳ) የበረራ ተቆጣጣሪ የሆኑት ዛም ዛም፥ ግድቡ ያለ አንዳች የውጭ ድጋፍ መገንባቱ የሚያኮራ ነው ብለዋል።

ዛም ዛም ኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፥ ግድቡ ቀጣናዊ ትስስርን በማሳለጥ ረገድ ዓይነተኛ ሚና እንደሚጫወት ገልጸው፤ የኃይል አቅርቦቱ በቀጣናው ያለውንኢንዱስትሪ ልማት እንደሚያፋጥነው አክለዋል።

በኬንያአካባቢ፣ አየር ንብረት ለውጥ እና ደን ልማት ሚኒስቴር የአየር ንብረት ለውጥ ምክትል ዳይሬክተር ሚካኤል ኦኩሙ በበኩላቸው፥ የኢትዮጵያ መንግሥት እንደዚህ ዓይነት ግዙፍ እና አስደናቂ ግድብ መገንባቱ ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል።

ግድቡ ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካውያን ትልቅ አበርክቶ እንደሚኖረውም ጠቁመዋል።

#Ethiopia #GERD #Inauguration