Search

የኢትዮጵያ ራዲዮ በየደረጃው ሀገራቸውን ያገለገሉ በርካታ ባለሙያዎችን ያፈራ ተቋም ነው

ቅዳሜ መስከረም 03, 2018 27

የኢትዮጵያ ሬዲዮ አሁን በሀገሪቱ ለሚገኙ በርካታ መገናኛ ብዙኃን አርዓያ መሆን የቻለ ትልቅ የሚዲያ ተቋም ነው ሲል የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ገለጸ።

የኢቢሲ አካል የሆነው እና ሥራ ከጀመረ 9 አስርት ዓመታትን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ ሬዲዮ 90ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን በማክበር ላይ ይገኛል።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዮናታን ተስፋዬ ከኢቲቪ ጋር በነበራቸው ቆይታ፥ አንጋፋው የኢትዮጵያ ሬዲዮ በቅኝ ግዛት ለማቀቁ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ድምፅ መሆን የቻለ ታሪካዊ ተቋም ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደ ሕዳሴ ግድብ ያሉ ገዢ ትርክቶችን መፍጠር ያስቻሉ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በድል እንደተወጣ አንስተው፤ በዚህ ሂደት የኢትዮጵያ ሬዲዮ የላቀ አስተዋጽኦ እንደነበረው አክለዋል።

በቀጣይም እንደ ኢትዮጵያ ሬዲዮ ያሉ አንጋፋ ሚዲያዎች እንዲያሳኳቸው የሚጠበቁ ትላልቅ አጀንዳዎች መኖራቸውን የጠቀሱት አቶ ዮናታን፤ ልዩነቶቻችንን ወደጎን በመተው አሰባሳቢ የጋራ ትርክቶች ላይ እንድናተኩር ከተቋሙ ብዙ ይጠበቃል ይጠበቃል ብለዋል።

ኢትዮጵያዊነትን በማቀንቀን ላለፉት 90 ዓመታት መንግሥት እና ሕዝብን ሲያገለግል የቆየው አንጋፋው ተቋም በየደረጃው ሀገራቸውን ያገለገሉ በርካታ ባለሙያዎችን ያፈራ መሆኑንም አንስተዋል።

በሜሮን ንብረት 

#EBC #ebcdotstrem #EthiopianRadio