Search

ሕዳሴ ግድብ በስኬት መጠናቀቁ በጋምቤላ ክልል እና ከተማ ነዋሪዎች ዘንድ ትልቅ ደስታን ፈጥሯል

እሑድ መስከረም 04, 2018 59

በጋምቤላ ክልል ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ በስኬት መጠናቀቁን በማስመልከት የጎዳና ላይ ሩጫ ተካሂዷል።

በዕለቱ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ በተገኙበት በጋምቤላ ከተማ የአካል ብቃት እንቅስቃሴም ተከናውኗል።

 

በመርሐ-ግብሩ ላይ ከከፍተኛ የመንግሥት ሀላፊዎች በተጨማሪ አትሌት ኢብራሂም ጄይላንን ጨምሮ የተለያዩ እንግዶችም ተሳትፈዋል።

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በሕዝቧ ርብርብ በስኬት መጠናቀቁ በጋምቤላ ክልል እና ከተማ ነዋሪዎች ዘንድ ትልቅ ደስታን ፈጥሯል።

ይህን ተከትሎም በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች ህብረተሰቡን ያሳተፉ የተለያዩ መርሐ-ግብሮች በመከናወን ላይ ናቸው።

በሚፍታህ አብዱልቃድር

#EBCdotstream #Ethiopia #GERD #PublicRally