Search

የቻይና የቴክኖሎጂ አቅም የፈጠረው የባህር ውስጥ የነዳጅ እና የጋዝ ማስተላለፊያ መስመር

ሰኞ መስከረም 19, 2018 26

ቻይና ባህር ውስጥ ነዳጅ እና የተፈጥሮ ጋዝን በማውጣት ጥቅም ላይ እያዋለች ይገኛል።
ሀገሪቷ ባህር ውስጥ የዘረጋችው የነዳጅ እና የጋዝ ማስተላለፊያ የቧንቧ መስመር አጠቃላይ ርዝመቱ 10 ሺ ኪሎ ሜትር ማለፉን አስታውቃለች።
የባህር ጨው እና የተለያዩ ኬሚካሎችን ተቋቁሞ ለዓመታት የሚቆየውን ይህ ግዙፍ የባንቧ መስመር ለማምረት እና ለመዘርጋት ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ወሳኝ ድርሻ እንዳላቸው ተጠቁሟል።
ቻይና ባለፉት 5 ዓመታት ባህር ውስጥ የዘረጋቻቸው የነዳጅ እና የጋዝ ማስተላለፊያ ቧንቧዎች ከ2 ኢንች እስከ 48 ኢንች የሚደርስ ስፋት እንደአላቸው ሲጂቲኤን ዘግቧል።
 
በጌትነት ተስፋማርያም