ኢትዮጵያ ያላትን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ፀጋ ለዓለም በበለጠ ጥራት ለማስተዋወቅ አዲስ ምዕራፍ ከፍታለች።
ላለፉት 17 ዓመታት የቆየው አሰራር ተሻሽሎ፣ በዘመናዊነት የታጀበው አዲሱ ብሔራዊ የቱሪዝም ፖሊሲ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ፅድቋል።
ይህ ፖሊሲ የኢትዮጵያን ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ጎዳና ላይ የሚያቆም ሲሆን፣ አምስት ዋና ዋና የለውጥ በሮችን ይከፍታል፦
ዘላቂ ልማት፦ ተፈጥሮን የማይጎዳና የአካባቢውን ማህበረሰብ በቀጥታ ተጠቃሚ የሚያደርግ አሰራር ይከተላል።
ለምን አስፈለገ?
የቀድሞው የ2001 ፖሊሲ አሁን ያለውን የቴክኖሎጂ ፍጥነትና የቱሪስቶችን ፍላጎት የማይመጥን በመሆኑ፣ ይህ ለውጥ የግድ ሆኗል።
ፖሊሲው ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ገቢን እንደሚያስገኝና ለሺዎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር የታመነበት ሲሆን፣ የኢትዮጵያን መልካም ገፅታም በላቀ ሁኔታ ይገነባል።
በየተመኙሽ አያሌው