Search

የኢትዮጵያ ቱሪዝም ከታሪክ ማህደር እስከ ዲጂታል አድማስ

ረቡዕ የካቲት 25, 2018 37

ኢትዮጵያ ያላትን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ፀጋ ለዓለም በበለጠ ጥራት ለማስተዋወቅ አዲስ ምዕራፍ ከፍታለች።
ላለፉት 17 ዓመታት የቆየው አሰራር ተሻሽሎ፣ በዘመናዊነት የታጀበው አዲሱ ብሔራዊ የቱሪዝም ፖሊሲ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ፅድቋል።
ይህ ፖሊሲ የኢትዮጵያን ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ጎዳና ላይ የሚያቆም ሲሆን፣ አምስት ዋና ዋና የለውጥ በሮችን ይከፍታል፦
👉አዳዲስ አማራጮች፦ ከታሪክ ባሻገር የቡና፣ የምግብ (Gastronomy)፣ የጀብዱ እና የኮንፈረንስ ቱሪዝም ልዩ ትኩረት ተሰጥቷቸዋል።
👉ዲጂታል ቱሪዝም፦ ቱሪስቶች አገልግሎትን በቴክኖሎጂ የሚያሳልጡበት "Smart Destinations" ይፈጠራሉ።
👉የጥራት ደረጃ፦ ከኤርፖርት እስከ መዳረሻዎች ያለው ሰንሰለት ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ እንዲሆን ጥብቅ የብቃት ማረጋገጫ ይዘረጋል።
👉የግል ዘርፍ ማበረታቻ፦ ለባለሀብቶች የፋይናንስ ተደራሽነትን ማመቻቸትና የቢሮክራሲ ማነቆዎችን ማስወገድ የፖሊሲው አካል ናቸው።
ዘላቂ ልማት፦ ተፈጥሮን የማይጎዳና የአካባቢውን ማህበረሰብ በቀጥታ ተጠቃሚ የሚያደርግ አሰራር ይከተላል።
ለምን አስፈለገ?
የቀድሞው የ2001 ፖሊሲ አሁን ያለውን የቴክኖሎጂ ፍጥነትና የቱሪስቶችን ፍላጎት የማይመጥን በመሆኑ፣ ይህ ለውጥ የግድ ሆኗል።
ፖሊሲው ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ገቢን እንደሚያስገኝና ለሺዎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር የታመነበት ሲሆን፣ የኢትዮጵያን መልካም ገፅታም በላቀ ሁኔታ ይገነባል።
በየተመኙሽ አያሌው