Search

የኢሬቻ ሆረ ፊንፊኔ ታዳሚዎች በዓሉ ወደሚከበርበት ኢሬቻ ፓርክ እየገቡ ነው

ቅዳሜ መስከረም 24, 2018 1652

ኢሬቻ ሆረ ፊንፊኔ እሴቱን ጠብቆ በአባገዳዎች መሪነት ንጋት ላይ በአዲስ አበባ በድምቀት ይከበራል።

የበዓሉ ታዳሚዎችም እየጨፈሩ እና ምስጋና እያቀረቡ በዓሉ ወደሚከበርበት ኢሬቻ ፓርክ እየገቡ ይገኛሉ። 

ኢሬቻ በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ ከጥንት ቅድመ አያቶቹ ጀምሮ ሕዝቡ ለፈጣሪ ምስጋና የሚያቀርብበት እና ሰላም የሚያጠናክርበት፣ ይቅርታ እና እርቅ የሚፈፀምበት በዓል ነው። 

ኢሬቻ የኅብረብሔራዊነት ማጠናከሪያ እንዲሁም የመቻቻል እና የአብሮነት ምልክት ነው።

በዓሉ ኢትዮጵያውያን በመካከላቸው እህትማማችነት እና ወንድማማችነትን የመያጠናክሩበትም ጭምር ነው።

ሆረ ፊንፊኔ እሴቱን ጠብቆ በነገው እለት በአባገዳዎች መሪነት የሚፈፀም ይሆናል። 

በላሉ ኢታላ

#EBC #Irreecha #Ethiopia #HoraFinfinnee