በኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት አንቀፅ 3 ከሰፈረው የሰንደቅ ዓላማ ድንጋጌ እንዲሁም በሰንደቅ ዓላማ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 863/2006 መሠረት ሰንደቅ ዓላማን በተመለከተ የተከለከሉ ተግባራት፦
👉🏽 ሰንደቅ ዓላማው በወጣበት ሰንደቅ (ምሰሶ ወይም ፖል) ላይ ማስታወቂያ መለጠፍ፣ ያለአግባብ ሌሎች ሰንደቅ ዓላማዎች ወይም አርማዎችን ጨምሮ ማውለብለብ ወይም መገልገል
👉🏽 ሰንደቅ ዓላማው ላይ ቃላትን መጻፍ፣ ሌሎች ምልክቶች ወይም አርማዎችን መጠቀም ወይም መገልገል
👉🏽 ሰንደቅ ዓላማውን በአዋጅ በተደነገገው መሠረት የተቀመጡ አርማውን ሳያካትቱ መጠቀም
👉🏽 ሰንደቅ ዓላማው በሚሰቀልበት እና በሚወርድበት ጊዜ ተገቢውን ክብር አለመስጠት
👉🏽 በስብሰባ ወይም በማናቸውም መሰል ክንውኖች ሰንደቅ ዓላማውን የጠረጴዛ ሽፋን አድርጎ መጠቀም
👉🏽 ሕዝብ በተሰበሰበበት ቦታ ሰንደቅ ዓላማውን በጽሑፍ ወይም በቃላት ወይም በድርጊት ወይም በሌላ በማናቸውም አኳኋን ማዋረድ ወይም ጉዳት እንዲደርስበት ማድረግ
👉🏽 የንደቅ ዓላማውን ቀለማት ቅደም ተከተል እንዲሁም የብሔራዊ አርማውን መጠን ሳይጠብቁ ማዘጋጀት እና መገልገል
👉🏽 በሰንደቅ ዓላማው አዋጅ ከተጠቀሰው የማውረጃ ጊዜ በላይ (ከፀሐይ መጥለቅ በኋላ) ተሰቅሎ እንዲቆይ ማድረግ እና በሰዓቱ አለመስቀል
👉🏽 ሰንደቅ ዓላማውን የሕንፃ ወይም የሌሎች ቁሳቁሶች መሸፈኛ ማድረግ
👉🏽 ሰንደቅ ዓላማውን በማንኛውም ንግድ ማስታወቂያነት መጠቀም ዋና ዋና የተከለከሉ ተግባራት ናቸው።
#EBC #ebcdotstream #EthiopianFlag #flag #nationalflagday