Search

በሀገር ግንባታ ሒደት ጨረስን ብሎ መቆም ሳይሆን ሁልጊዜም መትጋት እንደሚገባ ኮይሻ አመላካች ነው - ዶክተር መቅደስ ዳባ

እሑድ ጥቅምት 16, 2018 38

በሀገር ግንባታ ሒደት ጨረስን ብሎ መቆም እንደሌለ እና ለሀገር ልማት የሚውል ሥራ በመፈለግ ሁልጊዜም መትጋት እንደሚገባ የኮይሻ ፕሮጀክት ትምህርት ሆኗል ሲሉ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማን በኮይሻ ግድብ ከሚኒስትሮች ጋር አካሂደዋል።
በዚሁ ወቅት ዶክተር መቅደስ ዳባ፤ አንድ ሥራ ሲያልቅ ለሀገር ልማት የሚሆን ሌላ ውጤት መፈለግ እንደሚገባ ከፕሮጀክቱ ሥራ መረዳታቸውን አብራርተዋል።
በኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት፣ ሀገራቸውን የሚወዱ ጠንካራ ባለሙያዎች መኖራቸውን ገልፀው፤ ፕሮጀክቱ ቅልጥፍና፣ ትጋት እና ውጤታማነት የታየበት ትልቅ ሥራ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
ከዚህ በፊት ከፍተኛ ወጪ አስወጥተው ከውጭ ይገቡ የነበሩ ግብዓቶችን በራስ አቅም ማምረት የሚያስችል አቅም መፈጠሩን አንስተው፤ ይህን አቅም አጠናክሮ መቀጠል እንደሚያስፈልግም አመላክተዋል።
 
በቢታኒያ ሲሳይ