Search

የቡድን 20 ጉባኤ የአየር ንብረት ዓለም አቀፋዊ ቀውስ ላይ በትኩረት እንዲሠራ አሳሰበ

እሑድ ኅዳር 14, 2018 143

ትላንት የተጀመረው የቡድን 20 የመሪዎች ጉባኤ የአየር ንብረት ቀውሱን እና ሌሎች ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶችን የሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ በትኩረት እንዲሠራ አሳሰበ።

ለመጀመሪያ ጊዜ በአፍሪካ ምድር ጆሃንስበርግ ላይ የተካሄደው የቡድን 20 የመሪዎች ጉባኤ የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ በማሳለፍ ተጠናቅቋል፡፡

የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ቃል አቀባይ ቪንሰንት ማግዌንያ፤ የጉባኤው አጀንዳዎች ወደኋላ እንደማይመለሱ እና በትኩረት ተግባራዊ እንደሚደረጉ ገልጸዋል።

ቃል አቀባዩ ቪንሰንት ማግዌንያ አክለውም፣ "አጀንዳዎቹ ሁሉን ያማከሉ፣ አሳታፊ እና ወደ ተግባር የሚቀየሩ እንዲሆኑ ከዓመት በላይ ተደክሟል፤ ያለፈው ሳምንት ደግሞ ለቅመደ ዝግጅቱ ልዩ ትኩረት አድርገን ሠርተናል" ብለዋል።

ጉባኤው የመካከለኛው ምሥራቅ ጉዳዮችን ያየበት መንገድ አላሳመነኝም የምትለው አርጀንቲና አጀንዳው ላይ ጥርጣሬ እንዳላት ጠቅሳ፣ ለስብስቡ መንፈስ ግን እንደምትተባበር አስታውቃለች፡፡

ለመጀመሪያ ጊዜ በአፍሪካ ምድር የተካሄደውና ኢትዮጵያ ተጋባዥ ሆና የቀረበችበት የቡድን 20 የመሪዎች ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እያከናወነች ያለውን ሥራ ለጉባኤው አቅርባለች፡፡

በዚህ ረገድም ኢትዮጵያ እየተከተለችው ባለው መንገድ ዓለም ለአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ መፍትሔ እንዲያበጅ ጥሪ አስተላልፋለች፡፡

በለሚ ታደሰ

#Ebc #Ebcdotstream #Ethiopia #G20Summit