Search

ለሰላም ሲባል ዩክሬን የኔቶ አባልነት ጥያቄዋን ትተዋለች፡- ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዜለንስኪ

ሰኞ ታኅሣሥ 06, 2018 95

በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል ለዓመታት የዘለቀውን ጦርነት ለማስቆም "ለሰላም ሲባል ዩክሬን የኔቶ አባልነት ጥያቄዋን ትተዋለች" ሲሉ የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዜለንስኪ አስታወቁ፡፡
ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዜለንስኪ በአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ከተመራው ልዑክ እና ከአውሮፓ ሀገራት ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በጀርመኗ ከተማ በርሊን እየመከሩ ነው፡፡
ውይይቱ የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነትን ለማስቆም ያለመ ሲሆን ይህን ለማድረግ ያስችላል ተብሎ በተዘጋጀው የሰላም ስምምነት ላይ ያተኮረ ነው፡፡
በፕሬዚዳንቷ ተወክላ ውይይት እያደረገች ያለችው ዩክሬን ለዘላቂ ሰላም መስፈን ቁርጠኛ መሆኗን አስታውቃለች፡፡
በዚህም ለጦርነቱ መባባስ አንዱ ምክንያት የነበረው የኔቶ አባልነት ጥያቄዋን በጊዜያዊነት መሰረዟን አስታውቃለች፡፡
በምላሹም ደህንነቷ እና ስምምነቱ የተጠበቀ እንዲሆን ማድረግ ላይ ሀገራቱ ከጎኗ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርባለች፡፡
በተጨማሪም ከይዞታ ጋር የተያያዙ አለመስማማቶች ላይ ንግግሩ እንደሚካሄድ ነው የተጠቆመው፡፡
በአሜሪካ አስተባባሪነት እና በአውሮፓ ሀገራት ተሳትፎ የተዘጋጀው የሰላም ስምምነቱ ተኩስ አቁምን የመጀመሪያው ርምጃ በማድረግ የይዞታ ጥያቄዎችን፣ የደህንነት ዋስትና እንዲሁም የተጣሉ ማዕቀቦችን የሚዳስስ መሆኑን የሮይተርስ ዘገባ አስነብቧል፡፡
ከጉዳዩ ጋር ተያይዞ ከሩሲያ የተነሳ ሃሳብ ባይኖርም፣ በአውሮፓ ሀገራት በሚቃኝ ድርድር ላይ ሩሲያ የመገኘት ፍላጎት እንደሌላት ማስታወቋ የሚታወስ ነው፡፡
 
በአፎሚያ ክበበው
tions:
431