Search

በኢትዮጵያ ዳግም የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ

በኢትዮጵያ ደብረሲና አካባቢ በሬክተር ስኬል 4.6 ማግኒቲዩድ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ማዕከል አስታውቋል። 

ዓርብ ነሐሴ 02/2017 . ከሌሊቱ 7:18 ሰዓት የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ አቦምሳ፣ አዋሽ፣ ቆቦ እና ሮቢት አካባቢዎች ላይ መሰማቱን ነው መረጃው ያመለከተው።

በአዲስ አበባ አንዳንድ አካባቢዎችም ንዝረቱ እንደተሰማቸው ነዋሪዎች በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው እየገለጹ ይገኛሉ። 

#EBC #ebcdotstream #earthquake