Search

ኢትዮጵያ ሕልሟን ወደ እውነት የምትቀይር እና የምትኖር ሀገር መሆኗን በተግባር ያሳየ ፕሮጀክት

ቅዳሜ ጥር 23, 2018 251

የሸበሌ ሪዞርት ኢትዮጵያ የምታልም ብቻ ሳትሆን ሕልሟን ወደ እውነት የምትቀይር እና የምትኖር ሀገር መሆኗን በተግባር አሳይቷል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (/) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፣ ገበታ ለትውልድዐቢይ ፕሮጀክቶች መካከል ሁለተኛውን እና 385 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈውን የሸበሌ ሪዞርትን መርቀው ለአገልግሎት ማብቃታቸውን አስታውቀዋል።

ይህ ሪዞርት መዝናኛ ስፍራ ብቻ ሳይሆን፤ የዘመናዊ ሥነ-ሕንጻ ጥበብን ከሶማሌ ክልል ባሕላዊ እሴት ጋር አቀናጅቶ የያዘ የታሪክ ማኅደር እንደሆነ ነው የገለጹት።

ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ የገባነውን ቃል በተግባር ያረጋገጠ የምስራቁ የሀገራችን ክፍል ትልቅ ሥራ እንደሆነም አመላክተዋል።

በክልሉ የሚገኘው እጅግ ሰፊ እና ማራኪ ተፈጥሯዊ ጸጋ በመደመር ዕሴትና ትብብር ወደ ልማት ሲለወጥ፤ ኢትዮጵያ የምታልም ብቻ ሳትሆን ህልሟን ወደ እውነት የምትቀይር እና የምትኖር ሀገር መሆኗን በተግባር አሳይቷል።

#EthiopianBroadcastingCorporation #EBC #ebcdotstream #Ethiopia #Shebeleresort