አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 6 ሺህ 417 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት እያስመረቀ ይገኛል።
ዩኒቨርሲቲው እያስመረቀ የሚገኘው ለ76ኛ ዙር ያስተማራቸውን ተማሪዎች ሲሆን፣ ከተመራቂዎቹ መካከል 2 ሺህ 646 ሴቶች መሆናቸው ተመላክቷል።
በዚሁም በመጀመሪያ ዲግሪ 3 ሺህ 542፣ እና በሁለተኛ ዲግሪ 2 ሺህ 241 እንዲሁም የሦስተኛ ዲግሪ 377 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት እያስመረቀ መሆኑ ተገልጿል።