Search

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 6 ሺህ 417 ተማሪዎችን እያስመረቀ ነው

ቅዳሜ ሰኔ 20, 2018 74

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 6 ሺህ 417 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት እያስመረቀ ይገኛል።

ዩኒቨርሲቲው እያስመረቀ የሚገኘው 76 ዙር ያስተማራቸውን ተማሪዎች ሲሆን፣ ከተመራቂዎቹ መካከል 2 ሺህ 646 ሴቶች መሆናቸው ተመላክቷል።

በዚሁም በመጀመሪያ ዲግሪ 3 ሺህ 542 እና በሁለተኛ ዲግሪ 2 ሺህ 241 እንዲሁም የሦስተኛ ዲግሪ 377 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት እያስመረቀ መሆኑ ተገልጿል።