Search

ባሕር ዳር እና የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ነው

ቅዳሜ ሰኔ 20, 2018 45

ባሕር ዳር እና የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲዎች በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች በዛሬው ዕለት እያስመረቁ ነው።

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ሲያሰለጥናቸው የቆዩ 6 ሺህ 492 ተማሪዎችን እያስመረቀ ይገኛል።

ከተመራቂዎች መካከል 1 ሺህ 691 የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውን ከዩኒቨርሲቲው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

በሌላ በኩል የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሦስተኛ ዲግሪ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ 45 ተማሪዎች እያስመረቀ እንደሚገኝ አሚኮ ዘግቧል።