Search

ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ እንዲረዳ እየተከናወነ ያለው ዲፕሎማሲያዊ ግፊት ትክክለኛ ነው - አቶ ጌታቸው በቀለ

እሑድ ነሐሴ 04, 2017 133

የወደብ ጉዳይ ቀጣዩ የዓለም የሰላምና ጸጥታ ጉዳይ እየሆነ በመምጣቱ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትኩረት መስክ ሆኗል ሲሉ የዓለም አቀፍ ገበያ አማካሪ የሆኑት አቶ ጌታቸው በቀለ ተናገሩ፡፡

በቱርክሜኒስታን በተካሄደውተመድ በማደግ ላይ ያሉ የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ጉባኤ ላይ እየተነሱ የነበሩ ነጥቦች ጉዳዩ ትኩረት እንዲያገኝ እየተሰራበት መሆኑን ያሳየ መሆኑንም አቶ ጌታቸው ገልፀዋል፡፡

ወደብ የሌላቸው ሀገራት በዓለም የማይታዩ እየሆኑ ነው ሲል የገለጸው ተመድ፤ ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ምን ያህል እየሰራበት መሆኑን አመላካች ነው ብለዋል አማካሪው፡፡

ኢትዮጵያም 120 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ይዛ ወደብ አልባ ሆና መቀጠል እንደማትችልና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጉዳዩን እንዲረዳት እየሰራች ያለው ዲፕሎማሲዊ ግፊት ትክክለኛ ነው መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ ለባህር በር የጂኦግራፊ ቅርበት ያላትና በታሪክም 30 ዓመታት በፊት የወደብ ባለቤት የነበረች ሀገር መሆኗን ያነሱት አቶ ጌታቸው፤ ላነሳችው ጥያቄ ከሁሉም ሀገራት ቀድማ ተቀባይነት ማግኘት አለበት ብለዋል፡፡

ወደብ አልባ ሆኖ መቆየት የንግድ ወጪን ያበዛል፣ መዋእለ ንዋይን ይቀንሳል እንዲሁም ዲጂታል ክፍታትን ይፈጥራል ሲሉም አቶ ጌታቸው በኢቢሲ የቅዳሜ መልክ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል፡፡

በመሀመድ ፊጣሞ

#ebcdotstream #seaaccess #ethiopia #LLDC3